በኢትዮጵያ ሀገር በቀል የአባት እናት አምላክ አምልኮ እምነት ተቋም አማኞች እነደ ባህላ ቸው አና እሴታቸው ሃገራዊ በሆነ ልማድ ከአንድ ፈጣሪ በመንፈስ የሚገናኙበትና ሀይማኖትን ዘርን ቋነቋን ሳይለይ በአንድነት ተሰብስበው አንዱን አምላክ የሚያመለኩበት የጥንት የጠኋት ቀደምት እምነት ነው፡፡
እምነቱ በቅዱስ መንፈስ ቀጥተኛ ምሪት በቃል የሚመራ ቢሆንም አመስት መሰረታዊ ሃሳቦች ላይ ያተኩራል
1 እግዚያብሄር(God) ሰማይን መሬትን እንዲሁም በሰማይና ምድር ያለውን ሁሉ የፈጠረ የአማልክት ሁሉ አምላክ) አንድ አምላክ
2 ውቃቢ አምላክ (gad) ከእግዚያብሄር ውሰጥ የሚወጡና ( ለያንዳዳቸው የራሳቸው ህይወት ያላቸው ሆነው ግን ከአንድ መንፈስ ባህር የተጨለፉ አንድም ብዙም የሆኑ) የወጡበትን የእግዚያብሄርን ክብር የሚያሰጠብቁና የሰው ለጆችን የሚጠበቅ ቅዱስ መንፈስ
3 ባለውቃቢ ፤ በእግዚያብሄር የተመረጠና መንፈሱ የሚወርድበት (ምድር ላይ ላለው ፍጥረት ሁሉ በመንፈሱ እኩል የሚፈርድ) ሰው
4 ፅድቅን መጠበቅ ( በእግዚያብሄር መንፈስ መመራት)
5 ከሃጢያት መጠበቅ( አግዚያብሄር የፈጠረውን ህይወት ሁሉ ማክበር መጠበቅ)
በእነዚህ አምስት ፅነሰ ሃሳቦች ውሰጥ የሚመራ የጥንት የጠኋት እምነት ነው፡፡
የአባት እናት አምላክ አምልኮ በአንድ አምላክ አምልኮ ስርአት ውሰጥ ቀደምት ከክርስቶስ ልደት በፊት ይከናወን ከነበረው የገዳ ስርዓት ከወቄፈታ ሀይማኖት ጋር በአምልኮ ስርዓቱ ተመሳሳይነት ያለው ቢሆንም ዋቄ ፈታ እራሱን የቻለ ሀይማኖታዊ ስርአት ሲሆን የአባት እናት አምላክ አምልኮ የውቃቢ አምነት ከማንኛውም ቀደምት ሃይማኖት ተከታይ የሆነ ሰው በራሱ መንፈስና እግዚያብሄር ሰውን እነዲያገለግሉ መንፈሱን የሰጣቸው ባለውቃቢዎች አማካኝነት ከአንድ አምላክ ጋር ግንኙነት በመፍጠር ህመማቸውን እንዲሁም ኢከኖሚዊና ማህበራዊ ችግሮቻቸውን የሚፈቱበት አምልኮታዊ ክንውን ነው፡፡ የአባት እናት አምላክ አምልኮ አምነት በወቄፈታ እነደ አንድ የእምነቱ አካል የሚከናወን ዋና የአምለኮቱ ስርዓት ሲሆን በኦርቶዶክስ አና በእስልምናው ሀይማኖተች ዘነድ በተከታዮቹ ላይ በሚደረስው ጥላቻና የሃሰት ትምህረቶች መክኒያት ብዛት ያለው አማኝ በሚሰጥር አምነቱን በየቤቱ ያካሂዳል፡፡